tg-me.com/nibab_lehiwot/168
Last Update:
የእኔ ታሪክ ምዕራፍ 2
ክፍል -10
እሽ ቀጥይ ከዛስ ሕዝቅኤል በጣም ለማወቅ ጓጓ። ከዛማ ስለሱ ሰምቼ ጋር አላውቅም። ግን ምናልባት ጥሩ ቦታ ይሆናል ያለው ከእኛ መራቁ ጥሩ ነው ።ግን አላመንኩሽም ሜሪ አንቺስ ታዲያ ከዛ በኋላ ወለድሽ.....እኔማ አንድ ወንድና አንዲት ቆንጆ ሴት ልጆች አሉኝ። ከባለቤቴ ጋር ወደ አሜሪካ ተመለስን ጥሩ ህይወት እየኖርን ነው። ግን ማቲ ትዝ አይልሽም ሕዝቅኤል ፈገግ አለ። ሜሮንም እንደ መሽኮርመም እያደረጋት እውነት ሕዝቄ አንድ ቀን ከሀሳቤ ወጥቶ አያውቅም በህልሜ እንኳን ሳላየው ያደርኩባቸው ቀናት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። አብርሽስ.....ሰላምስ......ግን ታስታውሱኝ ነበር? ወይስ ከነመፈጠሬ ረስታችሁኛል??? ሜሮን ስለቤተሰቡ ድጋሚ አንስታ ቁስሉን መቀስቀስ ስላልፈለገች ወሬውን በአጭሩ ለመግታት ስትል ሁል ጊዜ ሕዝቄ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ብቻ ግን ተወው እኛም ያልተነገረ ብዙ መከራን አሳልፈናል። ማለፉ መልካም ነው ትላለች እማዬ። አንተስ ወለድክ አለችው ቀና ብላ እያየችው። አወ አንዲት ቆንጆ ሴት ልጅ አለችኝ አላት ፈገግ ብሎ ድንገት ግን ከ ራቢያ የወለደው ልጅ በአእምሮው መጣ እና አንድ ወንድ ልጅም አለኝ ምናልባት ራቢያ ከነገረችሽ።
አወ ነግራኝ ነበረ። ግን ለምን ዝም አልክ እሱምኮ አባት ያስፈልገዋል። አይ ሜሪ እኔ ለ እሱ አባት ለመሆን የምገባ ሰው አይደለሁም። ራቢያም አትፈልግም ተይው አባቱን አባቴ እያለ ይኑር አላት እዝን ብሎ። በዚህ ቅፅበት አንድ ሰው በር አንኳኩቶ ገባ። ሜሮን ስታየው ደርቃ ቀረች።
ሰላም ዋላችሁ አባባ ቪቪያንን ፈልጌ ነበር። አለ አንገቱን በሀፍረት እንደሰበረ።ሕዝቅኤል ቪቪያንን ስላሳዘናት በአሌፍ ቢያዝንበትም። የመለያየት ሀሳቡ ከሱ ስለመጣ ግን ብዙ ቂም አልያዘበትም።
" ሰ....ሰሚር " አለችው እየተወዛገበች። ሕዝቅኤል ሰሚር የሚለውን ስም ሲሰማ ልቡ ራደ።እንዴ የምን ሰሚር ነው አሌፍ ነው እንጅ.....አላት እየተወዛገበ ወይዘሮ ሜሪ እዚህ ምን ትሰሪያለሽ ? አንተ ራሱ እዚህ ምን ትሰራለህ? ወይ ጉድ ሁለቱም እየተፋጠጡ ነው። ሕዝቅኤል ሁለቱንም አስቀምጧቸው የት እንደሚተዋወቁ ሜሮንን ጠየቃት። የእናቱ ጓደኛ እንደሆነች አጭር መልስ ነገረችው።እናንተስ የት ተዋወቃችሁ አለችው። እየተገረመች የቪቪያን ጓደኛ ነው አላት ፈገግ ብሎ.........ወይ ጉድ ብላ ዝም አለች። አሌፍ እሷን ትቶ ሕዝቅኤልን አባባ ላናግርወት ፈልጌ ነበር ቀን መርጠው ቢነግሩኝ ? በትህትና ጠየቀው። ሕዝቅኤል የአሌፍን ስብዕና ከሁሉም በላይ በጣም ይወድለታል። ምናልባት እምነታቸው ባይለያይ ኖሮ ቪቪያንን ከሱ ውጭ ሌላ አታገቢም ብሎ በከለከላት ነበር። ብቸኛ ጭንቀቱ የ እምነት ልዩነት ነው።
ነገ ከሰዓት አለው አሌፍም ስራ ስላለኝ ልሂድ ብሎ ተሰናብቷቸው ወጣ።
ሕዝቄ ግን ይሔንን ልጅ ከዚህ በፊት አታውቀውም?
ሜሪ ደሞ ብዙ አመት ነውኮ ከ ቪቫ ጋር እንደልጄ ነው የማየው።
አይ አይ ሌላ ቦታ.....
አታወዛግቢኝ የት????
ይቀጥላል ..............
@nibab_lehiwot
BY ሕይወትን - በገፅ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/168